February 15, 2026

ዛሬ የዓመቱ መጨረሻ አይደለም!

የመጨረሻው ጫፍ ላይ ስንደርስ የማንከፋው የታክሲ ሰልፍ ላይ ብቻ ይመስለኛል። ምናልባት ሌላም ሊኖር ይችላል።የዓመቱ መጨረሻ ቀን ላይ መሆን ደግሞ እንደ እኔ በዓመቱ መጀመሪያ ቀን ላይ ሆኖ ብዙ ለመሥራት ለራሱም ለሌሎችም ቃል ገብቶ ላልፈጸመ ሰው ከምንም በላይ አስደንጋጭ ነው። ዛሬ የመጨረሻው ጫፍ ላይ ከመድረሳችን በፊት የመጀመሪያው ጫፍ ላይ ሆነን በዚህ ዓመት ብዙ መሥራት አስበን ከነበረ ምን […]

ዛሬ የዓመቱ መጨረሻ አይደለም! Read More »

የነቢያት ትንቢት የተፈጸመው በዚህ ቦታ ነው፤ አንዱ ስለሁሉ የሞተው በዚህ ተራራ ላይ ነው።

ለዓለም ሁሉ ሕይወትን የሚሰጠውን ገደሉት።ታመው ሳሉ የፈወሳቸውን ሰቀሉት፤ “አልጋህን ተሸክመህ ሂድ” ብሎ ያዘዛቸውን መስቀል አሸከሙት። እንዴት ያለ ጭካኔ ነው?ለዐርባ ዓመታት በቃዴስ በረሀ ከዓለት የፈለቀ ውኃ ያጠጣቸው እርሱ አልነበረምን?እነሱ ግን ከዕለታት አንድ ቀን “ተጠማሁ” ቢላቸው ሆምጣጤ አጠጡት። በግብፅ ሳሉ ሞት ከፈረዱባቸው የግብፅ ነገሥታት ያዳናቸውን ከጲላጦስ ሞቱን ለመኑለት። ፀሐይ ከሰዎች በለጠ፤ ጨረቃም ፈጣሪውን አወቀ።መላእክት በዐውደ መስቀል ቆመው

የነቢያት ትንቢት የተፈጸመው በዚህ ቦታ ነው፤ አንዱ ስለሁሉ የሞተው በዚህ ተራራ ላይ ነው። Read More »

ዓይነ ከርም(የጉዞ ማስታወሻ ክፍል አንድ)

በተራራማው የኤፍሬም ርስት የምትገኘው ዓይነ ከርም ከቦታው ስፋት የታሪኳ ብዛት ይገርመኛል የካህኑ ዘካርያስ ቤት በዚያ ይገኛል። “በ እግዚአብሔር ፊት ሁለቱም ጻድቃን ነበሩ” የተባለላቸው እነዚያ ቅዱሳን የሚኖሩበት ቅዱስ ተራራ ተሳለምሁት። እመቤታችን እዚህ ቦታ ለመድረስ ሁለት መቶ ሃያ ኪሎ ሜትር ተጉዛለች። ስትመጣ አረጋዊው ዮሴፍ ለንግድ ሩቅ አገር ሂዶ ስለነበር የተከተላት ሰው አልነበረም። መላእክት በቀኝና ግራ አጅበዋት ከናዝሬት

ዓይነ ከርም(የጉዞ ማስታወሻ ክፍል አንድ) Read More »

የአብርሃም ድንኳን(የጉዞ ማስታወሻ ክፍል ሁለት)

የአብርሃም ድንኳን የተተከለው ወዴት ነበር?ርብቃ ለያዕቆብ ታጭታ ስትመጣ ይስሐቅ የጠበቃት ከ እነዚህ ተራሮች በየትኛው ላይ ሆኖ ይሆን? ያዕቆብ ከቤርሳቤህ ወደ ካራን የሄደው በየት በኩል ይሆን?ለመጀመሪያ ጊዜ ሰው ለፈጣሪው መሠዊያ የሠራባት ዘፍ 12፥8 ቤቴል በኋላም ታላቁ መሥዋዕት ኢየሱስ ክርስቶስ የተሠዋባት ቀራንዮ ዛሬም አለች። በመጽሐፍ “አብርሃም ቤቴልን ወደ ምሥራቅ ጋይን ወደ ምዕራብ አድርጎ ድንኳኑን ተከለ ወደ ዓዜብም

የአብርሃም ድንኳን(የጉዞ ማስታወሻ ክፍል ሁለት) Read More »

የንጉስ ቀለበት

እግዚአብሔር የሚወደውን ስጦታ ዛሬ ተቀበለ። የማያበድሩት ባለጠጋ፣ የማይሾሙት ንጉስ ነው። ነገር ግን ቸር ነውና ሰውን ከመውደዱ የተነሳ ከሰው ስጦታን ይቀበላል። ሰውም በእግዚአብሔር ካለው መተማመን የተነሳ ከእግዚአብሔር ተቀብሎ ለእግዚአብሔር መባ ያቀርባል። ሕጻናት ከወላጆቻቸው ገንዘብ ተቀብለው ለወላጆቻቸው ስጦታ እንደሚያቀርቡት ያለ ነው። ዛሬ ወደ ቤተ እግዚአብሔር የቀረበችው ስጦታ እመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም ናት። ጸሐይና ጨረቃ በተፈጠሩ ቀን መላእክት

የንጉስ ቀለበት Read More »

በስእሏ ፊት ስቆም. . .

ሰማይና ምድርን የፈጠረ የሰማያዊ ንጉሥ የኢየሱስ ክርስቶስ እናቱ እመቤቴ ሆይ! መተዳደፍ በበዛበት ዓለም ስኖር ንጽሕናዋን እንዳላሳጣት ነፍሴን በአንቺ ዘንድ አኖራታለሁ፤ እግዚአብሔር ልጁን ወደ ዓለም በላከው ጊዜ ማረፊያ ያደረገው አንቺን ነውና ካንቺ የከበረ ቦታ ለነፍሴ ስለማላገኝላት በአንቺ ዘንድ አኖራታለሁ። የአብ ሙሽራ እመ አምላክ ሆይ! ወደ አንቺ እጆቼን ዘርግቼ ጸሎቴን አደርሳለሁ፤ዓይኖቼን ቀና አድርጌ ልመናዬን አቀርባለሁ፤ “የልብሱን ጫፍ

በስእሏ ፊት ስቆም. . . Read More »

“በቅዳሴ አፉን የፈታው ሕጻን”

በቅዳሴ አፉን የፈታ ሕጻን ይኼውላችሁ። ምስጋናን እየተመገበ ያደገውን ብላቴና ታዩት ዘንድ ኑ! በሕጻናት ልማድ አበ፣ እመ ብሎ አፍን መፍታት የተለመደ ነበር “ስብሐት ለአብ ስብሐት ለወልድ ስብሐት ለመንፈስ ቅዱስ” ብሎ ንግግሩን የጀመረ የዚህን ሕጻን ነገር ማሰብ ያስደንቃል። ለጌታስ ሁሉ ይቻለዋል “ ከሕጻናትና ከሚጠቡት አፍ ምስጋናን ለራስህ አዘጋጀህ” ተብሎ ተጽፏልና። ከታናሽነቱ ጀምሮ መንፈስ ቅዱስ ያደረበትን ይህንን የጸጋ

“በቅዳሴ አፉን የፈታው ሕጻን” Read More »

እረኛችን

እረኞች በምስጋና የተቀበሉት መልካሙ እረኛ ኢየሱስ ክርስቶስ ዛሬ ስለ መልካም እረኝነቱ ቤተ ክርስቲያን ታመሰግነዋለች። እንደዚህ ያለ እረኛ የት ይገኛል? ሕዝቡን ይጠብቃቸው ዘንድ ወደ ዓለም በመምጣቱ እረኛችን እንለዋለን እንጂ እንደምናውቃቸው እረኞች ያለ ባሕርይ የለውም። የዚህ ዓለም እረኛ ሲጠብቅ ኖሮ ከተኵላ ቢያድነውም ራሱ አርዶ ይበላዋል። ከሌባ ጠብቆ ቢያድነውም ራሱ ይሸጠዋል። ከበላተኛ የሚጠብቀው ራሱ ሊበላው ነው። ተንከባክቦ የሚያሳድገው

እረኛችን Read More »

ሥጋ የለበሰው እሳት

አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ለተጸነሰባት ለዚያች ሰዐት ለዚያች ቀን ምስጋና ይገባታል። ኢዮብ መከራ በገጠመው ጊዜ የተወለደበትን ቀን ረገመ፤ “ያ የተወለድሁበት ቀን ይጥፋ፥ ያም ወንድ ልጅ ተጸነሰ የተባለበት ሌሊት። ያ ቀን ጨለማ ይሁን እግዚአብሔር ከላይ አይመልከተው፤ ብርሃንም አይብራበት” ኢዮ. 3፥3 አለ። እኛ ደግሞ ደስታችን ለጀመረባት ለዚህች ቀን ምስጋና እናቀርብላታለን። ድንግል በድንግልና ሳለች ለፀነሰችበት ለዚህ ቀን አንክሮ

ሥጋ የለበሰው እሳት Read More »

በመንፈስ ቅዱስ ተፀነሰ፣

በግብረ መንፈስ ቅዱስ ተወለደ። ዛሬ ደግሞ በመንፈስ ቅዱስ መወለድን የምታሰጠንን ጥምቀት መሠረተልን። ከእኛ በተወለደ ጊዜ ለማደሪያ የሚሆን ስፍራ አላገኘምና በከብቶች በረት ተወለደ፤ እኛ ግን በጥምቀት ከእሱ ስንወለድ መኖሪያችን በሰማይ ነውና ሰማይ ተከፍቶ አየነው። ትናንት በልደቱ ከሰማይ ወደ ምድር መጣ፤ ዛሬ በጥምቀቱ ሁላችንን ወደ ሰማይ ይዞ ወጣ። በ ኢትዮጵያና ከኢትዮጵያ ውጭ ያላችሁ ውድ የጉባኤ ቤታችን አስተባባሪዎች፣

በመንፈስ ቅዱስ ተፀነሰ፣ Read More »